ግብርናችንን ለማዘመን፤ ከጠፋሁበት ተመልሻለሁ!


በዚህ ብሎግ ሥር ግብርናን በተመለከተ በተለያዩ ርዕሶች በተከታታይ አጫጭር ጽሁፎች አቀርባለሁ። እነዚህ ጽሑፎች የሚያተኩሩት እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያለዉ ህዝባችን በሚተዳደርበትና የኔም የሙያ መስኬ በሆነዉ ግብርና ላይ የራሴን አስተዋጽዖ ለማበርከት ነዉ። የዛሬዉ እነሆ፤

ከጠፋሁበት ተመልሻለሁ!!

የጠፋሁት ከምጽፈዉ ብሎጌ እንጂ ከመኖሪያ ሥፍራዬ ወይም ከሥራ ገበታዬ አይደለም፡፡ የመጨረሻ ጽሑፌን የጻፍኩት መጋቢት 15 ቀን 2012 ዓ.ም. (March 24, 2020) የኮሮና በሽታ በግብርናችን ላይ የሚያደርሰዉን አሉታዊ ጎን በሚመለከት ነበር፡፡ ይኸን የመጨረሻ ጽሑፌን የጻፍኩት ከ33 ወራት በፊት ማለትም የዛሬ 1000 ቀናት መሆኑ ነዉ፡፡  ለዚህ ረጅም ጊዜ መጥፋቴ ለኔም በጣም ይገርመኛል፡፡

ለመጥፋቴ አንዱ ምክንያት ይኸዉ ከኮሮና ጋር የተገናኘ የእንቅስቃሴ ገደብ ሊሆን ይችላል፡፡ ኮሮና በግብርናችን ላይ ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ በኑሮአችን ማለትም በጉዞአችን፣ በትምህርታችን፣ በሥራችን፣ በኢኮኖሚያችን ወ ዘ ተ በአለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ የሆነ እክል አድርሶብናል፡፡  የኮሮና ሁኔታዎች ሲሻሻሉ ግን በሌላ አቅጣጫ ትኩረት አድርጌ ስለነበር ብሎጌን መጻፍ ረሳሁ፡፡ አሁን ግን አዲስ ተስፋ ሰንቄ ተመልሼ መጥቻለሁ፡፡

በሚቀጥለዉ በሌላ ጽሑፍ እስክንገናኝ መልካሙን እመኛለሁ።

ዘሪሁን ታደለ፣ ከበርን ከተማ ስዊዘርላንድ፣ ታህሳስ 11፣ 2015 ዓ.ም. (December 20, 2022)

አስተያየት ያስቀምጡ