ግብርናችንን ለማዘመን፤ ሲምፖዚየም ለግብርና ምሁራን

በዚህ ብሎግ ሥር ግብርናን በተመለከተ በተለያዩ ርዕሶች በተከታታይ አጫጭር ጽሁፎች አቀርባለሁ። እነዚህ ጽሑፎች የሚያተኩሩት እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያለዉ ህዝባችን በሚተዳደርበትና የኔም የሙያ መስኬ በሆነዉ ግብርና ላይ የራሴን አስተዋጽኦ ለማበርከት ነዉ። የዛሬዉ እነሆ፤

ምፖዚየም ለግብርና ምሁራን

Advances in Agricultural Sciences ተብሎ የተሰየመዉ ሁለተኛዉ ሲምፖዚየም አዲስ አበባ በሚገኘዉ የግብርና ምርምር የስብሰባ አዳራሽ ጥቅምት 14፣ 2012 ዓ.ም. (እ. ኤ. አ. ኦክቶበር 25, 2019) ተካሂዶ ነበር። የዚህ ዓይነቱ የመጀመሪያዉ ሲምፖዚየም የተካሄደዉ ከአምስት ዓመታት በፊት እ.ኤ.አ. ኦክቶበር 24 በ2014 ሲሆን የተካሄደበትም ሥፍራ ይኸዉ የግብርና ምርምር የስብሰባ አዳራሽ ነበር።  ለማስታወስ ያህል መጀመሪያ በነበረዉ ሲምፖዚየም ጽሑፎቻቸዉን ያቀረቡትና የጽሁፎቻቸዉ ርዕሶች የሚከተሉት ነበሩ።

  1. ፕሮፌሰር ገቢሳ እጀታ (ፐርዱ ዩኒቨርስቲ፣ አሜሪካ) Research for development (R4D): Mantra or Practice?
  2. ፕሮፌሰር ተስፋዬ መንግሥቴ (ፐርዱ ዩኒቨርስቲ፣ አሜሪካ) Application of translational research for crop improvement
  3. ዶክተር ይልማ ከበደ (ቢል እንደ ሜሊንዳ ጌትስ ፋዉንዴሽን፣ አሜሪካ) Lessons learned from a career in research and development: a personal experience
  4. ዶክተር መላኩ ገድል (አይ አይ ቲ ኤ፣ ናይጄሪያ) Contributions of International agricultural research centers to research and development of national agricultural research systems
  5. ዶክተር ዘሪሁን ታደለ (በርን ዩኒቨርስቲ፣ ስዊዘርላንድ) Transcending the status quo ante of tef research

ጽሑፎቹ ከቀረቡ በኋላ በአምስቱ የጽሑፍ አቅራቢዎች የፓናል ውይይት የተደረገ ሲሆን የፓናል ውይይቱን የመሩት አንጋፋዉ ምሁር ዶክተር ብርሃኔ ገብረኪዳን ነበሩ። ይህን የመጀመሪያዉን ሲምፖዚየም በንግግር የከፈቱት በወቅቱ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዳይሬክቴር ጄኔራል የነበሩት ዶክተር ፈንታሁን መንግሥቱ ሲሆኑ ሲምፖዚየሙን የዘጉት ደግሞ በወቅቱ የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር የነበሩት ዶክተር አዱኛ ዋቅጅራ ናቸዉ።

በአሁኑ ሁለተኛዉ ሲምፖዚየም ወደ 200 የሚጠጉ ከተለያዩ መንግሥታዊም ሆነ መንግሥታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች የተዉጣጡ ምሁራን ተሳትፈዋል። በሲምፖዚየሙ መግቢያ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት ስምፖዚየሙን ያዘጋጁትና የዚህም ብሎግ ጸሐፊ የሆኑት በስዊዘርላንድ ሀገር የሚገኘዉ የበርን ዩኒቨርስቲ ባልደረባ የሆኑት ዶክተር ዘሪሁን ታደለ ናቸዉ። ስምፖዚየሙን በንግግር እንዲከፍቱ የተጋበዙት ደግሞ ዶክተር ብርሃኔ ገብረኪዳን ናቸዉ። ዶክተር ብርሃኔ በአገር አቀፍ ሆነ በአለም አቀፍ ደረጃ ያበረከቱትን አስተዋጽኦ በሚመለከት በዚሁ ብሎግ ሥር በተከታታይ አራት ጽሑፎች መቅረባቸዉ ይታወሳል። በዚሁ የመክፈቻ ንግግራቸዉ ዶክተር ብርሃኔ ስለ አገር በቀል ሰብሎች፣ ስለ ብዝሀ ህይወት ጥበቃ፣ ከፍተኛ ምርት ስለሚሰጡ ዝሪያዎች አስፈላጊነት፣ ስለ ሣይንስና ሥልጠና አስፈላጊነት እንዲሁም ትኩረት ሊደረግባቸዉ ስለሚገቡ ነጥቦች በዝርዝር አቅርበዋል።

ጥቅምት 14 ቀን 2012 ዓ.ም. በአዲስ አበባ የተካሄደዉ የሁለተኛዉ ሲምፖዚየም ተሳታፊዎች

በዚሁ የአንድ ቀን ሲምፖዚየም ሰባት ምሁራን በሁለት ምድብ ተከፍለዉ ጽሑፎቻቸዉን ያቀረቡ ሲሆን ሁለት የፓናል ውይይቶችም ተካሂደዋል። የመጀመሪያዉ ምድብ የአየር ንብረት ለዉጥና ቴክኖሎጂ የሚል ሲሆን ጽሑፎቻቸዉን ያቀረቡት ምሁራንና የጽሑፎቻቸዉ ርዕሶች የሚከተሉት ናቸዉ።

  1. ፕሮፌሰር ሰብስቤ ደምሰዉ (አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ) Future of coffee farming in different climate change scenarios in Ethiopia
  2. ዶክተር ታደለ ተፈራ (ኢ ሲ ፔ፣ አዲስ አበባ) Harnessing multiple benefits of push-pull technology in Ethiopia
  3. ዶክተር ግርማ ታቦር (ኮርቴቫ፣ አሜሪካ) Biotechnology for the benefit of agriculture and society
ሲምፖዚየሙን በንግግር የከፈቱት ዶክተር ብርሃኔ ገብረኪዳን (በስተግራ) እና በቡናችን ላይ የተደቀነዉን አደጋ ያወጉን ፕሮፌሰር ሰብስቤ ደምሰዉ (በስተቀኝ)።
  • 4.  ፕሮፌሰር የሆሹዋ ሳራንጋ (ሂብሩ ዩኒቨርስቲ ጄሩሳሌም፣ እስራኤል) Ancestral QTL alleles from emmer wheat enhance drought resistance & productivity of modern wheat

ከአራቱ ጽሑፎች ቀጥሎ በተደረገዉ የፓናል ውይይት የተሳተፉት ከላይ ጽሑፎቻቸዉን ያቀረቡት አራቱ ምሁራንና የአዲስ አበባ ሣይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ባልደረባ የሆኑት ዶክተር አዳነ አብርሃም ሲሆኑ የፓናል ውይይቱን የመሩት የመቀሌ ዩኒቨርስቲዉ ፕሮፌሰር ምትኩ ኃይሌ ናቸዉ።

የፓናል አንድ ተሣታፊዎች (ከግራ ወደ ቀኝ)፤ ሺራን ቤንዜቭ (የፕሮፌሰር የሆሹዋ ሳራንጋ ተወካይ)፣ ዶክተር ግርማ ታቦር፣ ፕሮፌሰር ምትኩ ኃይሌ (አወያይ)፣ ፕሮፌሰር ሰብስቤ ደምሰዉ፣ ዶክተር ታደለ ተፈራ እና ዶክተር አዳነ አብርሃም።

በሁለተኛዉ ምድብ የቀረቡት ጽሑፎች የጄኔቲክስና የዕጽዋት ሣይንስ የወደፊት ተስፋ የሚል ሲሆን ጽሑፎቻቸዉን ያቀረቡ ምሁራንና የጽሑፎቻቸዉ ርዕሶች የሚከተሉት ናቸዉ።

  1. ዶክተር ናኦሚ ናካያማ (ዩኒቨርስቲ ኦፍ ኤዴንብራ፣ እንግሊዝ) Touch-based enhancement of crop resilience: applying mugifumi to cereals
  2. ዶክተር ታካዮሺ ኢሺ (ቶቶሪ ዩኒቨርስቲ፣ ጃፓን) Chromosome elimination in plant wide hybridization for sustainable agriculture in future dryland
  3. ፕሮፌሰር ጆን ማኬይ (ኮሎራዶ ስቴት ዩኒቨርስቲ፣ አሜሪካ) Plant genetics to adapt to and reduce climate change (በቪዲዮ ኮንፈረንስ)

ከሶስቱ ጽሑፎች ቀጥሎ በተደረገዉ ሁለተኛዉ የፓናል ውይይት የተሳተፉት ከላይ ጽሑፎቻቸዉን ካቀረቡት ሶስት ምሁራን በተጨማሪ ዶክተር ጥልዬ ፈይሳ (አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ) እና ዶክተር መላኩ ገድል (አይ አይ ቲ ኤ፣ ናይጄሪያ) ሲሆኑ የፓናል ውይይቱን የመሩት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲዉ ፕሮፌሰር እንዳሻዉ በቀለ ናቸዉ።

የፓናል ሁለት ተሣታፊዎች (ከግራ ወደ ቀኝ)፤ ዶክተር ታካዮሺ ኢሺ፣ ዶክተር መላኩ ገድል፣ ፕሮፌሰር እንዳሻዉ በቀለ (አወያይ)፣ ዶክተር ናኦሚ ናካያማ፣ ዶክተር ጥልዬ ፈይሳ እና ፕሮፌሰር ጆን ማኬይ (በቪዲዮ ኮንፈረንስ)

የፓናል ሁለት ተሣታፊዎች (ከግራ ወደ ቀኝ)፤ ዶክተር ታካዮሺ ኢሺ፣ ዶክተር መላኩ ገድል፣ ፕሮፌሰር እንዳሻዉ በቀለ (አወያይ)፣ ዶክተር ናኦሚ ናካያማ፣ ዶክተር ጥልዬ ፈይሳ እና ፕሮፌሰር ጆን ማኬይ (በቪዲዮ ኮንፈረንስ)

በመጨረሻም የግብርና ምርምር ዳይሬክቴር ጄኔራል ዶክተር ማንደፍሮ ንጉሤ የመዝግያ ንግግር በማድረግ ሲምፖዚይሙ በታቀደለት ሰዓት ከቀኑ 11 ሰዓት ተጠናቋል። በሲምፖዚየሙ በቀረቡት ጽሑፎችና በፓናል ውይይት ሰለተደረገባቸዉ ነጥቦች በሌላ ብሎግ እጽፋለሁ።

በሚቀጥለዉ በሌላ ጽሑፍ እስክንገናኝ መልካሙን እመኛለሁ።

ዘሪሁን ታደለ፣ ከበርን ከተማ ስዊዘርላንድ፣ ጥቅምት 21፣ 2012 ዓ.ም. (November 1, 2019)

2 thoughts on “ግብርናችንን ለማዘመን፤ ሲምፖዚየም ለግብርና ምሁራን

  1. A great initiative to bring together ag scientists from Ethiopia and abroad to inform, educate, and possibly start lasting partnerships to continually address the tech issues that could impact Ethiopian agriculture. Thanks for the effort.

    Like

አስተያየት ያስቀምጡ