ግብርናችንን ለማዘመን፤ ቀለማት ምንን ይወክላሉ?

በዚህ ብሎግ ሥር ግብርናን በተመለከተ በተለያዩ ርዕሶች በተከታታይ አጫጭር ጽሁፎች አቀርባለሁ። እነዚህ ጽሑፎች የሚያተኩሩት እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያለዉ ህዝባችን በሚተዳደርበትና የኔም የሙያ መስኬ በሆነዉ ግብርና ላይ የራሴን አስተዋጽዖ ለማበርከት ነዉ። የዛሬዉ እነሆ፤

በግብርና ቀለማት ምንን ይወክላሉ?

የቀለማት አጠቃቅም በዓለማችን በተለይ በቢዝነሱ መስክ በከፍተኛ ጥንቃቄ ይሰራል። ምክንያቱም በማስታወቂያ ወይም በዌብ ሳይት የምንጠቅማቸዉ ቀለማት ደንበኛን በመሳብም ሆነ በማራቅ አስተዋጾኦ ስለሚያደርጉ ነዉ።

የዛሬዉ ጽሑፌ በቀለማት አመራረጥ ላይ ለማተኮር ሳይሆን በተለምዶ ከግብርና ጋር በተያያዘ በሰፊዉ ጥቅም ላይ የዋሉ የቀለማት ዓይነት ላይ ነዉ።  የምንጠቅማችዉ ሰብሎችና እንስሳት በሚመለከት የተለመዱ ቀለማትና የሚወክሏቸዉ ሴክተሮች ከዚህ በታች ቀርበዋል።

  • አረንጓዴ          ለምግብ የሚሆኑ ሰብሎች
  • ቢጫ              የቅባት ሰብሎች
  • ወርቃማ          አትክልትና ፍራፍሬ
  • ነጭ               ወተት
  • ሰማያዊ           ዓሣ
  • መዳብ            ዶሮና ዕንቁላል
  • ቀይ               ሥጋና ቲማቲም
  • ዳለቻ             ማዳበሪያ

ከቀለማት የተለያ ሰያሜ ያላቸዉም አሉ። ለምሳሌ፣

  • ክብ               ድንችን ይወክላል።
ከላይ በሥዕሉ እንደሚታየዉ የተለያዩ ቀለማት ከግብርና ጋር የተገናኙ የተለያዩ ሴክተሮችን ይወክላሉ።

በሀገራችን ታዋቂ ሰብሎቻችንን ለመግለጽ ከምንጠቀምባቸዉ ቀለማት ዉስጥ ሁለቱን ከዚህ በታች ማየት ይቻላል።

  • ነጩ ወርቃችን              ጥጥን ለማመልከት ሲሆን ጨዉንም ለማመልከት ጥቅም ላይ ይዉላል
  • ቡኒዉ ወርቃችን             ቡናን ለማመልከት እንጠቀምበታለን።

በኔ ግምት ከሁለትና ሦስት አሥርት ዓመታት በፊት ቡና የሀገሪቱን እስከ 60% የሚሆነዉን የዉጭ ምንዛሪ ያስገኝ ነበር። በዚያን ወቅት ነበር “የኢኮኖሚ ዋልታ ቡና ቡና…” የሚል መዝሙርም የተዘመረለት።

†

እዚህ በሥዕሉ የሚታየዉ የኢትዮጵያን ቡና ሻጮች የሚስተዋዉቁበት ማስታወቂያ ሲሆን “ወርቃማዉ ቡና ሙሉ በሙሉ ከኢትዮጵያ የመጣ” በሚል ተጽፎበታል። የዚህ ማስታወቂያ ዋናዉ መልዕክት ኢትዮጵያ የምታመርተዉ በተጠቃሚዎች ዘንድ ተወዳጅ የሆነዉን የአረቢካ ቡና ብቻ ስለሆነ ለሽያጭ የቀረበዉ ቡና ከሌላ የቡና ዓይነት ጋር አለመደባለቁን ያሳያል። ሌላዉ ደግሞ ኢትዮጵያ የቡና መገኛ ሀገር በመሆኗ ተጠቃሚዎች ከዚህ የቡና መነሻ ከሆነች ሀገር የመጣ ቡናን ሲጠጡ ከፍተኛ እርካታ እንደሚሰማቸዉ ስለሚታወቅ ነዉ። በዚሁ መሠረት የዚህ ቡና የመሸጫ ዋጋዉ ከፍ ይላል።

ባሁኑ ጊዜ ቡና ለኢትዮጵያ ከ30-35% የሚሆነዉን የዉጭ ምንዛሪ ብቻ ያስገኛል። ወደ ውጭ የሚላከዉ ቡና መጠን ቀነሰ ወይስ ሌላ ምክንያት ተፈጠረ? በሚቀጥለዉ ጽሑፌ ይህንን በተመለከተ ለመጻፍ እሞክራለሁ።

እስከዚያው በቸር ይግጠመን።

ዘሪሁን ታደለ፣ ከበርን ከተማ ስዊዘርላንድ፣ ሰኔ 2፤ 2011 ዓ.ም.

አስተያየት ያስቀምጡ